የሴቶች ወቶችና ህፃናት ዳይሬክቶሬት ተግባርና ኃላፊነት

  • የሴቶችና ወጣቶችን እኩል ተሳታፊነትና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ፣ እንዲሁም የህጻናት በመብትና ደህንነት ለማስጠቅ የሚያስችል ለሴክተሩ ተጠሪ በሆኑ ተቋማት የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት
  • የሴቶችንና የወጣቶችን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነትን ለማሳደግና የህጻናት መብትና ደህንነት ለማረጋገጥ እና የህጻናትን ተሳትፎ ለማሳደግ የባለድርሻ አካላትን አቅም ማጐልበት
  • የማካተቻውን ተግባራዊነት በየ6 ወሩ በመገምገም ለሚመለከተው አካል ሪፖርት ማቅረብ፣
  • በተቋሙ የሥርዓተ-ፆታን ክፍተት ለመሙላት የአቅም ግንባታ ሥራዎችን ማከናወንና የሴቶችንና ወጣቶችን ማብቃት
  • የተቋሙ የስራ ሂደቶች ሥርዓተ-ፆታን በእቅድ ዝግጅት፣ አፈፃፀም ክትትልና ግምገማ አካተው ተግባራዊ ማድረጋቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችል የክትትልና ድጋፍ ሥርዓት በመዘርጋት ተፈጻሚ ማድረግ፣
  • በፆታ የተተነተነ መረጃ አደራጅቶ መያዝ፣
  • በአፈጻጸም ሂደት የተገኙ ግብዓቶችን በማሰባሰብ ማካተቻውን እንዳስፈላጊነቱ ማሻሻል፣